የዳያስፖራ ቢዝነስ ሳምንት
በዩናይትድ ኪንግደም እና ሰሜን አየርላንድ ለምትገኙ ኢትዮጵያውያና ትውልድ ኢትዮጵያውያን የንግድ ተቋማት ባለቤቶች በሙሉ
“Rising Ethiopia” በሚል መሪ ቃል ከዲሴምበር 20 ቀን 2020 እስከ ፌብርዋሪ 21 ቀን 2021 ኢትዮጵያ አገራችን በቱሪዝም፣ በንግድ እና በኢንቨስትመንት መስኮች ያሏትን እምቅ ሀብቶች ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ የሚያስተዋውቅ የማህበራዊ ሚዲያ ዘመቻ በዩኬ ነዋሪ በሆኑት ዶ/ር በላቸው ተስፋ ሀሳብ አመንጪነት፣ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስተባባሪነትና በባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር፣ በቱሪዝም ኢትዮጵያ፣ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን እንዲሁም በሁሉም አገራት ባሉ የኢትዮጵያ ኤምባሲዎች ተሳትፎ የተጀመረ ሲሆን የዚሁ ዘመቻ አካል የሆነው “Diaspora Business Week” ከጃንዋሪ 25 እስከ ጃንዋሪ 31 ቀን 2021 ይካሄዳል፡፡
ይህ ዘመቻ በየአገራቱ የሚገኙ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አባላት የንግድ ተቋማት ማለትም ሪስቶራንቶች፣ ሱቆች፣ የጤና ተቋማት፣ አማካሪ ድርጅቶች፣ የህግ፣ የበረራ፣ የአካወንቲንግ፣ የጋራጅና የታክሲ እንዲሁም የሌሎች አገልግሎት ሰጪ ድርጅቶች አገልግሎታቸውና ምርቶቻቸውን በ”Rising Ethiopia”፣ በኤምባሲዎች እና ከላይ በተጠቀሱ የመንግስት ተቋማት ማህበራዊ ሚዲያዎች በነጻ የሚያስተዋውቁበት መድረክ ነው፡፡ መድረኩ ተቋማቱ ስለአገልግሎታቸው እና ምርቶቻቸው መረጃ ለሰፊው ዳያስፖራ ማህበረሰብ እና ለውጭ ዜጎች በማቅረብ የገበያ ዕድላቸውን ሊያሰፉ የሚችሉበት ዕድል የሚፈጥር ነው፡፡
በመሆኑም በዩናይትድ ኪንግደምና በሰሜን አየርላንድ የምትገኙና በዚህ ኩነት ላይ መሳተፍ የምትፈልጉ የንግድ ተቋማት ባለቤቶች በስልክ ቁጥር +447367109262/+447939956086 ተጨማሪ መረጃ ማግኘትና መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
ከሠላምታ ጋር
ተፈሪ መለሰ
አምባሳደር
-
የዳያስፖራ ቢዝነስ ሳምንት
በዩናይትድ ኪንግደም እና ሰሜን አየርላንድ ለምትገኙ ኢትዮጵያውያና ትውልድ ኢትዮጵያውያን የንግድ ተቋማት ባለቤቶች በሙሉ
Latest News
Browse allwe appreciate your help.