የኮቪድ-19 ወቅታዊ መረጃ፡ የቆንስላ አገልግሎት መጀመር አስመልክቶ የተዘጋጀ ማስታወሻ

5 Jun 2020

በእንግሊዝ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ስርጭት አስመልክቶ የታዩ ለውጦችን ከግምት በማስገባት ኤምባሲያችን አገልግሎቱን አስመልክቶ ያስቀመጣቸውን የጥንቃቄ እርምጃዎች ለተገልጋዮች ማሳወቅ አስፈልጓል።

በዚህ ወቅት የጤና እና ደህንነት የሁሉም ሰው ጉዳይ እና ቅድሚያ ተሰጥቶት ሊታሰብበት የሚገባ መሆኑ ታምኖበት፣ኤምባሲው የእለት ከእለት ስራዎችን በሚያከናውንበት ወቅት የተገልጋዮችን እና የሰራተኞችን ደህንነት ቅድሚያ ሰጥቶየሚሰራ ይሆናል።

የስራ ቦታ አካባቢ ደህንነት ለማስጠበቅ እና ቅድመ መከላከልን በማጠናከር የማህበረሰብ ጤና ሳይንስ መመሪያን መሰረት በማድረግ የጥንቃቄ እርምጃዎች እየተወሰዱ ይገኛሉ። በዚህም መሰረት ኤምባሲያችን የሚከተለውን የስራ ጊዜ ሰሌዳ እና መመሪያ አውጥቷል።

የቆንስላ አገልግሎት የስራ ሰዓት

ከሰኞ እስከ አርብ
ጊዜ፡ ከ10.00 am – 4.00 pm

እ.ኤ.አ ጁን 08/2020 ጀምሮ የኤምባሲያችን ቆንስላ ክፍል ለተገልጋዮች ክፍት እንደሚሆን በማሳወቅ የሚከተሉትን አገልግሎቶች በቀጠሮ ብቻ የሚያስተናግድ ይሆናል።

  • ቪዛን በተመለከተ የዲፕሎማቲክ እና ሰርቪስ ቪዛ አገልግሎት ብቻ የሚሰጥ ይሆናል። በሌላ ማስታወቂያ እስከሚገለፅ ድረስ ሌሎች መደበኛ የቪዛ ጥያቄዎች ለሚፈልጉ ደንበኞች በተከታዩ ድረ-ገፅ በመግባት ማመልከት ይቻላል https://www.evisa.gov.et ወይም በአዲስ አበባ ቦሌ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የመዳረሻ(On arrival) ቪዛ ማግኘት የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን።
  • አዲስ የመታወቂያ ካርድ ማመልከቻዎች (ዘወትር ሰኞ እና አርብ)
  • አዲስ የፓስፖርት ማመልከቻዎች (ዘወትር ረቡዕ እና አርብ)
  • ሌሴፓሴ እና ሌሎች የጉዞ ሰነዶች (ዘወትር ረቡዕ እና አርብ)
  • የውክልና ሰነዶች (ዘወትር ማክሰኞ እና ሃሙስ) የሚስተናገዱ ይሆናል

 

 ያለቀጠሮ የሚመጡ ተገልጋዮች የሚፈልጉትን አገልግሎት ማግኘት እንደማይችሉ ግንዛቤ በመውሰድ ያለቀጠሮ ለሚመጡ ተገልጋዮች በሌላ ጊዜ አዲስ ቀጠሮ እንዲይዙ በማድረግ በተያዘላቸው የቀጠሮ ቀንመሰረት የሚስተናገዱ ይሆናል።  መጉላላትና ቅሬታ እንዳይኖር በተከታዩ ስልክ ቀጠሮ ማስያዝ ይቻላል 0207 838 3877

 

በሌላ ማስታወቂያ እስኪገለፅ ድረስም የሚከተሉትን አገልግሎቶች በፖስታ ብቻ የምናስተናግድ መሆኑን እናሳውቃለን።

  • ፓስፖርት እድሳት
  • የትውልደ ኢትዮጵያዊ መታወቂያ ካርድ እድሳት እና
  • የሰነድ ማረጋገጥ አገልግሎቶች

በፖስታ እንዴት ማመልከት እንደሚገባ የእያንዳንዱን አገልግሎት ዝርዝር ጉዳይ በሚከተለው ድረ-ገፅ መመልከት ይቻላል www.ethioembassy.org.uk/consular-services

ለድንገተኛ ጉዳዮች በሚከተለው ስልክ ቁጥር በመደወል ምላሽ የሚሰጥ መሆኑን 0207 838 3898 ወይም በተከታዩኢሜይል መልዕክት ማድረስ ይቻላል ca@ethioembassy.org.uk። ለድንገተኛ ቀጠሮዎች የእያንዳንዱን ጉዳይ ምንነት መሰረት በማድረግ የሚከናወን ይሆናል።

ተጨማሪ አዳዲስ አሰራሮችና ተለዋጭ መመሪያዎች ሲኖሮ የሚገለፅ ይሆናል።

ለኤምባሲ ጎብኝዎች

በእንግሊዝ መንግስት ወቅታዊ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት የCOVID-19 ስርጭት አሁንም ከፍተኛ ጥንቃቄ እንደሚያስፈልገው በተደጋጋሚ ተጠቅሷል። ስለሆነም ለተገልጋዩና ላገልጋዩ ጤንነት ሲባል ቫይረሱን ለመከላከል የሚያስችሉ ጥንቃቄዎች ተግባራዊ እንዲደረጉ ምክራችንን እንቀጥላለን። በመሆኑም፡-

  • ማንኛውም አገልግሎት ፈላጊ ኤምባሲ ከመምጣቱ በፊት በተከታዩ ስልክ ቁጥር በመደወል ቀድሞ የቀጠሮ ጊዜ ሰሌዳ ማስያዝ ይጠበቅበታል ►0207 838 3877
  • የህመም ስሜት ያለበት፣ የኮቪድ-19 ምልክቶች ያሉበት፣ ወይም ደግሞ በቅርቡ ቫይረሱ በከፍተኛ ሁኔታ ካጠቃቸው አገሮች የመጣ እና ወደ ኤምባሲያችን ጉብኝት ማድረግ ለሚፈልግ ማንኛውም ደንበኛ/አገልግሎት ፈላጊ ከ14 ቀናት በኋላ ብቻ ለአገልግሎት መምጣት እንደሚገባ ግንዛቤ መውሰድ ያስፈልጋል። ይህ መልዕክት ከታመመ ሰውጋር ወይም ከኮቪድ-19 በሽተኛ ጋር ንክኪ ያላቸውን ሰዎችም ያጠቃልላል።
  • ወደ ኤምባሲ የሚመጣ ማንኛውም ደንበኛ/ተገልጋይ የፊት መሸፈኛ ወይም ጭምብል መልበስ ይጠበቅበታል።
  • ወደ ኤምባሲው ቅጥር ግቢ ከመግባት እና ከሰራተኞች ጋር ከመገናኘት በፊት እጅ መታጠብ/ሳኒታይዘር መጠቀም ያስፈልጋል።
  • ማንኛውም ጎብኝ/አገልግሎት ፈላጊ ኤምባሲ ግቢ ውስጥ ከሌሎች ሰዎች (የቤተሰብ አባላት ያልሆኑ) ጋር ቢያንስ የ2 ሜትር ርቀት በመጠበቅ መገልገል ይገባል።
  • በኤምባሲ ውስጥ የሚገኙ ቅፆች ሲሞሉ የራሶትን ብዕር ወይም እስክብሪቶ እንዲጠቀሙ ይመከራል።

ወደ ኢትዮጵያ የሚደረግ ጉዞ

እ.ኤ.አ አርብ፣ ማርች 13 /2020 ኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የኮቪድ-19 ታማሚ ማግኘቷን ያሳወቀች ሲሆን በዛሬው እለት ማለትም እ.ኤ.አ ጁን 05/2020፣ አጠቃላይ በበሽታው የተያዙ ሰዎች ቁጥር 1805 ደርሷል።

የኮቪድ-19 ወረርሺኝ ከተከሰተ ጀምሮ የኢትዮጵያ መንግስት የቫይረሱን መስፋፋት ለመከላከል የተለያዩ እርምጃዎችን እየወሰደ ይገኛል። የመንግስት የኮቪድ-19 መከላከያ እና ጥንቃቄ መመሪያ በተከታዩ ሊንክ ያገኙታል: www.ethioembassy.org.uk/travel-advisory

እ.ኤ.አ ከማርች 23/2020 ጀምሮ ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ ማንኛውም ተጓዥ መንግስት ባዘጋጃቸው የለይቶ ማቆያ ሆቴሎች እና ቦታዎች ለ14 ቀናት እራሳቸውን ለይተው እንዲያቆዩ እየተደረገ ይገኛል። ዲፕሎማቶች በራሳቸው ኤምባሲ ውስጥ ለ14 ቀናት እራሳቸውን ለይተው እንዲያቆዩ ይጠበቃል።

የ14 ቀን ለይቶ ማቆያ የተላላፊ (Transit) ተጓዦችን አይመለከትም። የTransit ተጓዦች ወደሌላ መዳረሻ የሚሄዱበት አየር መንገድ እስኪሳፈሩ ድረስ በስካይላይት ሆቴል እንዲቆዩ ይደረጋል።

Latest News

Browse all
27 Feb 2024
Notice
የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ኤምባሲ ለንደን የሚሸፍናቸው ሀገራት ነዋሪ ለሆናችሁ ሁለተኛ ትውልድ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የቀረበ ታላቅ ሀገራዊ ጥሪ! ክቡር የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ሁለተኛው ትውልድ የኢትዮጵያ ዳያስፖራዎች በሦስት ዙር ወደ ሀገራቸው በመግባት ኢትዮጵያን እንዲጎበኙ እና የባህል መሠረታቸውን እንዲያውቁ የቀረበውን ጥሪ በመቀበል የመጀመሪያው ዙር የጉዞ መርሃ ግብር የተጀመረ ሲሆን በዚህም በመላው ዓለም የሚገኙ በርካታ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው…
11 Jan 2024
Back To Your Origins
UK pledges to increase dev’t aid to 200 mln Euros Ethiopia and United Kingdom (UK) have finalized to ink the Memorandum of Understanding (MoU) to scale up the diplomatic ties to strategic partnership level, said Ethiopian Ambassador to UK. In an exclusive interview with The Ethiopian Herald, Ethiopian Ambassador to the UK Teferi Melesse said that the activities are ongoing…
9 Jan 2024
Ethiopia-UK ties to enter ‘new era’
The Embassy of the Federal Democratic Republic of Ethiopia in London wishes you a joyful holiday season and prosperous New Year.
31 Dec 2023
Happy New Year 2024!
we extend our warmest invitation to you for the highly anticipated 1st Dire International Technology Expo 2024. As an influential figure in the technology sector, your presence at this groundbreaking event would be highly valued. Date: Jan 24 to Jan 28 / 2024 Venue: Dire Dawa Youth Sports Center Website: http://www.direinttechexpo.com The first Dire International Technology Expo 2024 is poised…
27 Dec 2023
Dire International Tech Expo
22 Dec 2023
Festive Message from Ambassador Teferi Melesse Desta
በለንደን የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ኤምባሲ አስተባባሪነት ከዩናይትድ ኪንግደም ከሚገኙ የንግድና ዘርፍ ማህበራት ጋር በመቀናጀት እ.ኤ.አ ከዲሴምበር 13-15/2023 ባዘጋጀው የልምድ ልውውጥ ፕሮግራም 11 አባላትን የያዘ የኢትዮጵያ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት የልዑካን ቡድን በለንደን ከተማ ከሚገኙ 3 የብሪታንያ የንግድ ምክር ቤቶች ጋር የልምድ ልውውጥና የትብብር ግንኙነት ውይይት አደረጉ፡፡ ሶስቱ የንግድ ም/ቤቶች የብሪቲሽ ንግድ ም/ቤት፤ የብርቲሽ-ኢትዮጵያ ንግድ ም/ቤትና የለንደን ንግድ ም/ቤት ናቸው። በሶስቱም መድረኮች…
15 Dec 2023
የኢትዮጵያ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት የልዑካን ቡድን የለንደን ቆይታ
7 Dec 2023
Notice
The main office of the Global Black History, Heritage, and Education Centre (GBHHEC) will be officially established in Addis Ababa on Friday, December 08, 2023. Lead by Ambassador Teferi Melesse, Ethiopian Ambassador to the United Kingdom and North Ireland, a delegation of founding board members of the Global Black History, Heritage, and Education Centre (GBHHEC) landed in Addis Ababa. Director…
6 Dec 2023
Ethiopia will remain the center of important historical, cultural, and diplomatic initiatives.
በኤፕሪል 1973 ወደ ዩናይትድ ኪንግደም በረራውን ቦይንግ 720-ቢ አውሮፕላን በመጠቀም በሳምንት ለሁለት ቀናት የጀመረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአሁኑ ወቅት አጅግ ዘመናዊ የሆኑ ኤርባስ 350 እና ቢ787 ድሪምላይነር አውሮፕላኖችን በመጠቀም በሳምንት ለአስር ጊዜያት በቀጥታ በረራ እያካሄደ መሆኑ ተመልክቷል፡፡ በዚህም ከአስር ሺህ በላይ መንገደኞችን ወደ 60 አለም አቀፍ መዳረሻዎች እያጓጓዘ መሆኑን በዩናይትድ ኪንግደም እና አየርላንድ የአየር መንገዱ ጽ/ቤት አስታውቋል፡፡ በለንደን ሂትሮ እና…
23 Nov 2023
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ዩናይትድ ኪንግደም የሚያደርገውን በረራ በሳምንት ወደ አስር ጊዜያት ማሳደጉን አስታወቀ፡፡
On the sidelines of the Global Food Security Summit the Ethiopian Ambassador to UK H.E. Ambassador Teferi Melesse Desta met with British International Investment and AgDevCo to discuss potential investment and collaboration in Ethiopia. The Ambassador commended the work done with EthioChicken and explained the robust potential Ethiopia has attract even more investment.
21 Nov 2023
Ambassador Teferi met with BII and AgDevCo
We are excited to announce the inaugural flight of Ethiopian Airlines from Addis Ababa to Gatwick Airport landed earlier today! This new route marks an important milestone in Ethiopian Airlines commitment to providing convenient and seamless travel options for passengers between the UK and Ethiopia. We look forward to welcoming you on board as we connect the vibrant city of…
21 Nov 2023
Ethiopian Airlines Started new route to London Gatwick Airport.