ክቡር አምባሳደር ተፈሪ መለሰ በዌስት ሚኒስቴር የሁሉም ፓርቲዎች ፓርላሜንታዊ ቡድን አባላትና እንግዶች በተገኙበት ስለኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ እንደዚሁም ስላሉት የንግድ፣ የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም ዕድሎች ገለፃ አድርገዋል

3 Mar 2023

በእንግሊዝ የኢትዮጵያ አምባሳደር ክቡር ተፈሪ መለሰ በዌስት ሚኒስቴር የሁሉም ፓርቲዎች ፓርላሜንታዊ ቡድን አባላትና እንግዶች በተገኙበት ስለኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ እንደዚሁም ስላሉት የንግድ፣ የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም ዕድሎች ገለፃ አድርገዋል፡፡

በዚሁ ገለፃቸውም በደቡብ አፍሪካ፣ በኬንያና በአገር ውስጥ በተደረጉ ውይይቶች የተደረሱ ስምምነቶችን በመተግበር የተረጋጋና ሠላማዊ ሁኔታ በትግራይ ክልል ከመፈጠሩም በላይ መሠረታዊ አገልግሎቶችን ከማቅረብ በተጨማሪ የምግብ እህል፣ የህክምና ቁሳቁሶች እንዲሁም የባንክ የኤሌክትሪክና የስልክ አገልግሎቶች በስፋት እየተደረሰ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡ በመሆኑም አሁን የተደረሰበት ሠላም የበለጠ እየተረጋገጠ ህዝቡን ወደ መደበኛ ህይወት የመመለስና በጦርነቱ የወደሙ መሠረተ ልማቶችን መልሶ የመገንባት ሥራ በትኩረት እንደሚሠራ አስረድተዋል፡፡ በዚህም የእንግሊዝ መንግስትን ጨምሮ የዓለም ህብረተሰብ ድጋፉን እንዲለግስ እንደሚጠበቅ ገልፀዋል፡፡

ኢትዮጵያ እጅግ አዋጪ የሆኑ ሠፋፊ የኢንቨስትመንት ዕድሎች በግብርና፣ በማኑፋክቸሪንግ፣ አግሮፕሮሰሲንግ፣ በኢነርጂ፣ በጤና፣ በቱሪዝም እና በማዕድን ዘርፎች ያሏት ከመሆኗም በተጨማሪ የአፍሪካ ህብረት መቀመጫና በአፍሪካና በመካከለኛው ምስራቅና አውሮፓ ሀገራት ቅርብ ገበያ ናት፡፡ የህዝቧ ብዛት 120 ሚሊዮን እየደረሠ ሲሆን ከ60-70% የሚሆነውም ሠራተኛ ወጣት ኃይል እንደሆነ ተገልጿል፡፡ መንግስት የተለያዩ ሪፎርሞች በመሥራት ሀገሪቱ ለውጪ ኢንቨስትመንትና ንግድ የበለጠ የተመቸ ሁኔታ የተፈጠረባት ሆናለች፡፡ የንግድ ህግ ማሻሻያ፣ የካፒታል ገበያን ለመጀመር የህግ ማዕቀፍና ተቋም መፍጠር፣ የፋይናንስ ዘርፉ የውጪ ባንኮችን ተሣትፎ እንዲያካትት መደረግ፣ የኢንቨስትመንት ህግን ማበረታቻ ሥርዓት ማሻሻል፣ የቴሌኮም አገልግሎት ለግል ኢንቨስትመንት ክፍት መደረግ በዋናነት የሚጠቀሱ ናቸው፡፡ በዚህም የተወሰኑ የእንግሊዝ ኩባንያዎች በተለያዩ መስኮች በኢትዮጵያ በኢንቨስትመንት እየተሳተፉ ሲሆን የበለጠ እንዲሣተፉ የእንግሊዝ መንግስትም ማበረታታት እንደሚገባው ለፓርላማ አባላቱ ተገልጾላቸዋል፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድም መንገደኞችን በ120 አገራት የሚያገናኝ የበረራ መረብ የፈጠረ ሲሆን ዕቃዎችንና ማጓጓዝ በተመለከተ በ60 ሀገራት የካርጎ አገልግሎት ተደራሽ እያደረገ መሆኑ ለባለሀብቶቹና ለንግዱ ማህበረሰብ ተጨማሪ ዕድል መሆኑንም አስረድተዋል፡፡

በመጨረሻም ከተሣታፊዎች መለስተኛ ጥያቄዎች ተነስተው ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል፡፡ በማጠቃለያም የቡድኑ ሰብሳቢ የፓርላማ አባል የሆኑት ሎርድ ሎረንስ ሮበርትሠንና ሚስተር ቲም ጆንሰን ለኢትዮጵያ ያላቸውን ፍቅር እንደዚሁም ኢትዮጵያ ያላትን ዕድልና እያስመዘገበች ያለችውን የኢኮኖሚ ዕድገት በማንሣት አድናቆታቸውን ገልጸዋል፤ በቀጣይም የንግድ ልዑካን ቡድን ይዘው ወደ ኢትዮጵያ እንደሚሄድ ገልጸዋል፡፡

 

Latest News

Browse all
27 Feb 2024
Notice
የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ኤምባሲ ለንደን የሚሸፍናቸው ሀገራት ነዋሪ ለሆናችሁ ሁለተኛ ትውልድ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የቀረበ ታላቅ ሀገራዊ ጥሪ! ክቡር የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ሁለተኛው ትውልድ የኢትዮጵያ ዳያስፖራዎች በሦስት ዙር ወደ ሀገራቸው በመግባት ኢትዮጵያን እንዲጎበኙ እና የባህል መሠረታቸውን እንዲያውቁ የቀረበውን ጥሪ በመቀበል የመጀመሪያው ዙር የጉዞ መርሃ ግብር የተጀመረ ሲሆን በዚህም በመላው ዓለም የሚገኙ በርካታ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው…
11 Jan 2024
Back To Your Origins
UK pledges to increase dev’t aid to 200 mln Euros Ethiopia and United Kingdom (UK) have finalized to ink the Memorandum of Understanding (MoU) to scale up the diplomatic ties to strategic partnership level, said Ethiopian Ambassador to UK. In an exclusive interview with The Ethiopian Herald, Ethiopian Ambassador to the UK Teferi Melesse said that the activities are ongoing…
9 Jan 2024
Ethiopia-UK ties to enter ‘new era’
The Embassy of the Federal Democratic Republic of Ethiopia in London wishes you a joyful holiday season and prosperous New Year.
31 Dec 2023
Happy New Year 2024!
we extend our warmest invitation to you for the highly anticipated 1st Dire International Technology Expo 2024. As an influential figure in the technology sector, your presence at this groundbreaking event would be highly valued. Date: Jan 24 to Jan 28 / 2024 Venue: Dire Dawa Youth Sports Center Website: http://www.direinttechexpo.com The first Dire International Technology Expo 2024 is poised…
27 Dec 2023
Dire International Tech Expo
22 Dec 2023
Festive Message from Ambassador Teferi Melesse Desta
በለንደን የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ኤምባሲ አስተባባሪነት ከዩናይትድ ኪንግደም ከሚገኙ የንግድና ዘርፍ ማህበራት ጋር በመቀናጀት እ.ኤ.አ ከዲሴምበር 13-15/2023 ባዘጋጀው የልምድ ልውውጥ ፕሮግራም 11 አባላትን የያዘ የኢትዮጵያ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት የልዑካን ቡድን በለንደን ከተማ ከሚገኙ 3 የብሪታንያ የንግድ ምክር ቤቶች ጋር የልምድ ልውውጥና የትብብር ግንኙነት ውይይት አደረጉ፡፡ ሶስቱ የንግድ ም/ቤቶች የብሪቲሽ ንግድ ም/ቤት፤ የብርቲሽ-ኢትዮጵያ ንግድ ም/ቤትና የለንደን ንግድ ም/ቤት ናቸው። በሶስቱም መድረኮች…
15 Dec 2023
የኢትዮጵያ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት የልዑካን ቡድን የለንደን ቆይታ
7 Dec 2023
Notice
The main office of the Global Black History, Heritage, and Education Centre (GBHHEC) will be officially established in Addis Ababa on Friday, December 08, 2023. Lead by Ambassador Teferi Melesse, Ethiopian Ambassador to the United Kingdom and North Ireland, a delegation of founding board members of the Global Black History, Heritage, and Education Centre (GBHHEC) landed in Addis Ababa. Director…
6 Dec 2023
Ethiopia will remain the center of important historical, cultural, and diplomatic initiatives.
በኤፕሪል 1973 ወደ ዩናይትድ ኪንግደም በረራውን ቦይንግ 720-ቢ አውሮፕላን በመጠቀም በሳምንት ለሁለት ቀናት የጀመረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአሁኑ ወቅት አጅግ ዘመናዊ የሆኑ ኤርባስ 350 እና ቢ787 ድሪምላይነር አውሮፕላኖችን በመጠቀም በሳምንት ለአስር ጊዜያት በቀጥታ በረራ እያካሄደ መሆኑ ተመልክቷል፡፡ በዚህም ከአስር ሺህ በላይ መንገደኞችን ወደ 60 አለም አቀፍ መዳረሻዎች እያጓጓዘ መሆኑን በዩናይትድ ኪንግደም እና አየርላንድ የአየር መንገዱ ጽ/ቤት አስታውቋል፡፡ በለንደን ሂትሮ እና…
23 Nov 2023
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ዩናይትድ ኪንግደም የሚያደርገውን በረራ በሳምንት ወደ አስር ጊዜያት ማሳደጉን አስታወቀ፡፡
On the sidelines of the Global Food Security Summit the Ethiopian Ambassador to UK H.E. Ambassador Teferi Melesse Desta met with British International Investment and AgDevCo to discuss potential investment and collaboration in Ethiopia. The Ambassador commended the work done with EthioChicken and explained the robust potential Ethiopia has attract even more investment.
21 Nov 2023
Ambassador Teferi met with BII and AgDevCo
We are excited to announce the inaugural flight of Ethiopian Airlines from Addis Ababa to Gatwick Airport landed earlier today! This new route marks an important milestone in Ethiopian Airlines commitment to providing convenient and seamless travel options for passengers between the UK and Ethiopia. We look forward to welcoming you on board as we connect the vibrant city of…
21 Nov 2023
Ethiopian Airlines Started new route to London Gatwick Airport.