ከ 155 አመት በፊት ከመቅደላ ተዘርፎ የተወሰደው ጽላተ ቅድስት ድንግል ማሪያም ወ ቅዱስ ገብርኤል ታቦት ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ተመለሰ፡፡

24 Sep 2023

ከ 155 አመት በፊት ከመቅደላ ተዘርፎ የተወሰደው ጽላተ ቅድስት ድንግል ማሪያም ወ ቅዱስ ገብርኤል ታቦት ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ተመለሰ፡፡

ዛሬ ለንደን በሚገኘው ርዕሰ አድባራት ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን በተካሄደ ስነስርአት ርክክቡ ተከናውኗል፡፡

በእለቱ በለንደን የኢትዮጵያ ኤምባሲ ዲፕሎማቶች ፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ርእሰ አድባራት ለንደን ደብረጽዮን ቤተክርስቲያን የሃይማኖት አባቶች ፣ የብሄራዊ ቅርስ አስመላሽ ኮሚቴ ተወካይ ፣ ቅርሶቹን ለማሰመለስ የተባበሩ እና በዩናይትድ ኪንግደም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች ተገኝተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ልኡክን የመሩት መጋቢ ሀዲስ ቀሲስ አባተ ጎበና እንደተናገሩት ይህን ሃይማኖታዊና ታሪካዊ ፋይዳ ያለውን ታቦት ወደ ሀገሩ እንዲመለስ ከ ሁለት አመታት በፊት ጥረት መደረግ መጀመሩን አስታውሰው ፣ በለንደን የኢትዮጵያ ኤምባሲን ጨምሮ ፣ የብሄራዊ ቅርስ አስመላሽና ይሀው ታቦት ወደሀገሩ እንዲመለስ ድጋፍ ሲያደርጉ የነበሩትን የሼሄራዜድ በጎ አድራጎት መስራች እና ዶ/ር ጃኮብ ግኒሰኪን አመስግነዋል፡፡

ታቦቱ በተገቢው የሃይማኖት ስርአት ተይዞ ወደ ሀገሩ በቅርቡ እንደሚገባም ገልጸዋል፡፡

የብሄራዊ ቅርስ አስመላሽ ኮሚቴ ተወካይ ፕሮፌሰር አሉላ ፓንክረስት በበኩላቸው በብሪታኒያ ሙዚየሞች ከ አስር በላይ የኢትዮጵያ ታቦቶች ያሉ በመሆናቸው ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ፣ ኤምባሲው ፣ የጥናትና ምርምር ተቋማት ፣ የመንግስት ሃላፊዎችና የእምነቱ ተከታዮች በሙሉ የጀመሩትን የማስመለስ ጥረት አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል፡፡ታቦታቱ መንፈሳዊ ፋይዳቸው ለኢትዮጵያ ህዝብ እንጂ ለሙዚየም ባለመሆኑ ዛሬ በዚህ የርክክብ ስነስርአት ላይ የተገኛችሁ ሁሉ ይህን የማስመለስ ጥሪ እንድተቀላቀሉ ሲሉ ተናግረዋል፡።

ከታቦታቱ በተጨማሪ ሌሎች በርካታ ቅርሶች በግለሰቦችና በተለያዩ አካላት እጅ አሁንም ተይዘው ያሉ በመሆናቸው እሰኪመለሱ ግፊቱን አጠናክረን መቀጠል አለብን ብለዋል፡።

ለሁለት አመታት ታቦቱን ለማስመለስ ከኤምባሲው ፣ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያንና እና ከብሄራዊ ቅርስ አስመላሽ ኮሚቴ ጋር በግል ሲሰሩና ሲያስተባብሩ የቆዩት ዶ/ር ጃኮብ ግኒስኪን በበኩላቸው በኢትዮጵያ ከልጅነታቸው ጀምሮ ማሳለፋቸውን ተናግረው ኢትዮጵያ በልጅነቴ ለዋለችልኝ ውለታ ከዚህም በላይ ለመመለስ እጥራለሁ ብለዋል፡።

ከ 2000 በላይ ምእመናን የተሳተፉበት የዛሬው ስነስርአት የኢትዮጵያ ወዳጅ የሆኑ የውጪ ሀገራት ዜጎችና የአካባቢው ባለስልጣናት ተገኝተዋል ፡

Latest News

Browse all
27 Feb 2024
Notice
የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ኤምባሲ ለንደን የሚሸፍናቸው ሀገራት ነዋሪ ለሆናችሁ ሁለተኛ ትውልድ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የቀረበ ታላቅ ሀገራዊ ጥሪ! ክቡር የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ሁለተኛው ትውልድ የኢትዮጵያ ዳያስፖራዎች በሦስት ዙር ወደ ሀገራቸው በመግባት ኢትዮጵያን እንዲጎበኙ እና የባህል መሠረታቸውን እንዲያውቁ የቀረበውን ጥሪ በመቀበል የመጀመሪያው ዙር የጉዞ መርሃ ግብር የተጀመረ ሲሆን በዚህም በመላው ዓለም የሚገኙ በርካታ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው…
11 Jan 2024
Back To Your Origins
UK pledges to increase dev’t aid to 200 mln Euros Ethiopia and United Kingdom (UK) have finalized to ink the Memorandum of Understanding (MoU) to scale up the diplomatic ties to strategic partnership level, said Ethiopian Ambassador to UK. In an exclusive interview with The Ethiopian Herald, Ethiopian Ambassador to the UK Teferi Melesse said that the activities are ongoing…
9 Jan 2024
Ethiopia-UK ties to enter ‘new era’
The Embassy of the Federal Democratic Republic of Ethiopia in London wishes you a joyful holiday season and prosperous New Year.
31 Dec 2023
Happy New Year 2024!
we extend our warmest invitation to you for the highly anticipated 1st Dire International Technology Expo 2024. As an influential figure in the technology sector, your presence at this groundbreaking event would be highly valued. Date: Jan 24 to Jan 28 / 2024 Venue: Dire Dawa Youth Sports Center Website: http://www.direinttechexpo.com The first Dire International Technology Expo 2024 is poised…
27 Dec 2023
Dire International Tech Expo
22 Dec 2023
Festive Message from Ambassador Teferi Melesse Desta
በለንደን የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ኤምባሲ አስተባባሪነት ከዩናይትድ ኪንግደም ከሚገኙ የንግድና ዘርፍ ማህበራት ጋር በመቀናጀት እ.ኤ.አ ከዲሴምበር 13-15/2023 ባዘጋጀው የልምድ ልውውጥ ፕሮግራም 11 አባላትን የያዘ የኢትዮጵያ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት የልዑካን ቡድን በለንደን ከተማ ከሚገኙ 3 የብሪታንያ የንግድ ምክር ቤቶች ጋር የልምድ ልውውጥና የትብብር ግንኙነት ውይይት አደረጉ፡፡ ሶስቱ የንግድ ም/ቤቶች የብሪቲሽ ንግድ ም/ቤት፤ የብርቲሽ-ኢትዮጵያ ንግድ ም/ቤትና የለንደን ንግድ ም/ቤት ናቸው። በሶስቱም መድረኮች…
15 Dec 2023
የኢትዮጵያ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት የልዑካን ቡድን የለንደን ቆይታ
7 Dec 2023
Notice
The main office of the Global Black History, Heritage, and Education Centre (GBHHEC) will be officially established in Addis Ababa on Friday, December 08, 2023. Lead by Ambassador Teferi Melesse, Ethiopian Ambassador to the United Kingdom and North Ireland, a delegation of founding board members of the Global Black History, Heritage, and Education Centre (GBHHEC) landed in Addis Ababa. Director…
6 Dec 2023
Ethiopia will remain the center of important historical, cultural, and diplomatic initiatives.
በኤፕሪል 1973 ወደ ዩናይትድ ኪንግደም በረራውን ቦይንግ 720-ቢ አውሮፕላን በመጠቀም በሳምንት ለሁለት ቀናት የጀመረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአሁኑ ወቅት አጅግ ዘመናዊ የሆኑ ኤርባስ 350 እና ቢ787 ድሪምላይነር አውሮፕላኖችን በመጠቀም በሳምንት ለአስር ጊዜያት በቀጥታ በረራ እያካሄደ መሆኑ ተመልክቷል፡፡ በዚህም ከአስር ሺህ በላይ መንገደኞችን ወደ 60 አለም አቀፍ መዳረሻዎች እያጓጓዘ መሆኑን በዩናይትድ ኪንግደም እና አየርላንድ የአየር መንገዱ ጽ/ቤት አስታውቋል፡፡ በለንደን ሂትሮ እና…
23 Nov 2023
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ዩናይትድ ኪንግደም የሚያደርገውን በረራ በሳምንት ወደ አስር ጊዜያት ማሳደጉን አስታወቀ፡፡
On the sidelines of the Global Food Security Summit the Ethiopian Ambassador to UK H.E. Ambassador Teferi Melesse Desta met with British International Investment and AgDevCo to discuss potential investment and collaboration in Ethiopia. The Ambassador commended the work done with EthioChicken and explained the robust potential Ethiopia has attract even more investment.
21 Nov 2023
Ambassador Teferi met with BII and AgDevCo
We are excited to announce the inaugural flight of Ethiopian Airlines from Addis Ababa to Gatwick Airport landed earlier today! This new route marks an important milestone in Ethiopian Airlines commitment to providing convenient and seamless travel options for passengers between the UK and Ethiopia. We look forward to welcoming you on board as we connect the vibrant city of…
21 Nov 2023
Ethiopian Airlines Started new route to London Gatwick Airport.