ከ 155 አመት በፊት ከመቅደላ ተዘርፎ የተወሰደው ጽላተ ቅድስት ድንግል ማሪያም ወ ቅዱስ ገብርኤል ታቦት ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ተመለሰ፡፡

24 Sep 2023

ከ 155 አመት በፊት ከመቅደላ ተዘርፎ የተወሰደው ጽላተ ቅድስት ድንግል ማሪያም ወ ቅዱስ ገብርኤል ታቦት ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ተመለሰ፡፡

ዛሬ ለንደን በሚገኘው ርዕሰ አድባራት ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን በተካሄደ ስነስርአት ርክክቡ ተከናውኗል፡፡

በእለቱ በለንደን የኢትዮጵያ ኤምባሲ ዲፕሎማቶች ፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ርእሰ አድባራት ለንደን ደብረጽዮን ቤተክርስቲያን የሃይማኖት አባቶች ፣ የብሄራዊ ቅርስ አስመላሽ ኮሚቴ ተወካይ ፣ ቅርሶቹን ለማሰመለስ የተባበሩ እና በዩናይትድ ኪንግደም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች ተገኝተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ልኡክን የመሩት መጋቢ ሀዲስ ቀሲስ አባተ ጎበና እንደተናገሩት ይህን ሃይማኖታዊና ታሪካዊ ፋይዳ ያለውን ታቦት ወደ ሀገሩ እንዲመለስ ከ ሁለት አመታት በፊት ጥረት መደረግ መጀመሩን አስታውሰው ፣ በለንደን የኢትዮጵያ ኤምባሲን ጨምሮ ፣ የብሄራዊ ቅርስ አስመላሽና ይሀው ታቦት ወደሀገሩ እንዲመለስ ድጋፍ ሲያደርጉ የነበሩትን የሼሄራዜድ በጎ አድራጎት መስራች እና ዶ/ር ጃኮብ ግኒሰኪን አመስግነዋል፡፡

ታቦቱ በተገቢው የሃይማኖት ስርአት ተይዞ ወደ ሀገሩ በቅርቡ እንደሚገባም ገልጸዋል፡፡

የብሄራዊ ቅርስ አስመላሽ ኮሚቴ ተወካይ ፕሮፌሰር አሉላ ፓንክረስት በበኩላቸው በብሪታኒያ ሙዚየሞች ከ አስር በላይ የኢትዮጵያ ታቦቶች ያሉ በመሆናቸው ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ፣ ኤምባሲው ፣ የጥናትና ምርምር ተቋማት ፣ የመንግስት ሃላፊዎችና የእምነቱ ተከታዮች በሙሉ የጀመሩትን የማስመለስ ጥረት አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል፡፡ታቦታቱ መንፈሳዊ ፋይዳቸው ለኢትዮጵያ ህዝብ እንጂ ለሙዚየም ባለመሆኑ ዛሬ በዚህ የርክክብ ስነስርአት ላይ የተገኛችሁ ሁሉ ይህን የማስመለስ ጥሪ እንድተቀላቀሉ ሲሉ ተናግረዋል፡።

ከታቦታቱ በተጨማሪ ሌሎች በርካታ ቅርሶች በግለሰቦችና በተለያዩ አካላት እጅ አሁንም ተይዘው ያሉ በመሆናቸው እሰኪመለሱ ግፊቱን አጠናክረን መቀጠል አለብን ብለዋል፡።

ለሁለት አመታት ታቦቱን ለማስመለስ ከኤምባሲው ፣ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያንና እና ከብሄራዊ ቅርስ አስመላሽ ኮሚቴ ጋር በግል ሲሰሩና ሲያስተባብሩ የቆዩት ዶ/ር ጃኮብ ግኒስኪን በበኩላቸው በኢትዮጵያ ከልጅነታቸው ጀምሮ ማሳለፋቸውን ተናግረው ኢትዮጵያ በልጅነቴ ለዋለችልኝ ውለታ ከዚህም በላይ ለመመለስ እጥራለሁ ብለዋል፡።

ከ 2000 በላይ ምእመናን የተሳተፉበት የዛሬው ስነስርአት የኢትዮጵያ ወዳጅ የሆኑ የውጪ ሀገራት ዜጎችና የአካባቢው ባለስልጣናት ተገኝተዋል ፡

Latest News

Browse all
በኤፕሪል 1973 ወደ ዩናይትድ ኪንግደም በረራውን ቦይንግ 720-ቢ አውሮፕላን በመጠቀም በሳምንት ለሁለት ቀናት የጀመረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአሁኑ ወቅት አጅግ ዘመናዊ የሆኑ ኤርባስ 350 እና ቢ787 ድሪምላይነር አውሮፕላኖችን በመጠቀም በሳምንት ለአስር ጊዜያት በቀጥታ በረራ እያካሄደ መሆኑ ተመልክቷል፡፡ በዚህም ከአስር ሺህ በላይ መንገደኞችን ወደ 60 አለም አቀፍ መዳረሻዎች እያጓጓዘ መሆኑን በዩናይትድ ኪንግደም እና አየርላንድ የአየር መንገዱ ጽ/ቤት አስታውቋል፡፡ በለንደን ሂትሮ እና…
23 Nov 2023
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ዩናይትድ ኪንግደም የሚያደርገውን በረራ በሳምንት ወደ አስር ጊዜያት ማሳደጉን አስታወቀ፡፡
On the sidelines of the Global Food Security Summit the Ethiopian Ambassador to UK H.E. Ambassador Teferi Melesse Desta met with British International Investment and AgDevCo to discuss potential investment and collaboration in Ethiopia. The Ambassador commended the work done with EthioChicken and explained the robust potential Ethiopia has attract even more investment.
21 Nov 2023
Ambassador Teferi met with BII and AgDevCo
We are excited to announce the inaugural flight of Ethiopian Airlines from Addis Ababa to Gatwick Airport landed earlier today! This new route marks an important milestone in Ethiopian Airlines commitment to providing convenient and seamless travel options for passengers between the UK and Ethiopia. We look forward to welcoming you on board as we connect the vibrant city of…
21 Nov 2023
Ethiopian Airlines Started new route to London Gatwick Airport.
“We have no intention of threatening the sovereignty of any nation but we would like a rules based access to the Red Sea. Our request is to initiate discussions towards sustainable solutions.” “What we seek to accomplish as a nation requires clarity of thought. It also requires hard work on a daily basis. Although there are many issues contributing to…
14 Nov 2023
PM Abiy Ahmed Responds to MP’s
For all diaspora scholars interested in participating in technical and vocational colleges' short-term knowledge and skill transfer programs. Click the link for further detail: https://t.co/p5ExO5oiLn  or Download the PDF format: Document.
8 Nov 2023
Notice for Diaspora Scholars
ከ 184 በላይ የአለም ሀገራት በተሳተፉበትና በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ጎብኚዎች ፣ አለም አቀፍ እውቅና ያላቸው የተለያዩ ሀገራት አሰጎብኚዎች እና የጉዞ ጸሀፍት በተገኙበት በዚሁ አለም አቀፍ የጉዞ የገበያ ማእከል ኢትዮጵያ አለም አቀፍ እውቅና ካገኙ የቱሪስት ሀብቶቿ ጀምሮ አዳዲስ የቱሪስት መዳረሻዎቿን አስተዋውቃለች፡፡ የቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር አምባሳደር ናሲሴ ጫሊ ፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ፣የክልል ቱሪዝም ቢሮዎች ፣ ከ 16 በላይ የኢትዮጵያዊያን አስጎብኚ ድርጅቶች፣ ዳያስፖራውና…
7 Nov 2023
ኢትዮጵያ አዳዲስና ጥንታዊ የቱሪስት ሀብቷን ለንደን ኤክሴል በሚገኘው አለም አቀፍ የጉዞ ገበያ ማእከል ላይ አስተዋወቀች፡፡
The 42nd World Travel Market London 2023 Officially kicked off today at ExCeL London with the presence of H.E. Nasise Challi Jira of Ministry of Tourism-Ethiopia, H.E. Ambassador Teferi Melesse Desta of Embassy of Ethiopia, London, Mr. Henok from Ethiopian Airlines, Hailemelekot Mamo, v/p ET Holidays and Digital services and different tour operators from Ethiopia. It's being visited by multitude…
6 Nov 2023
World Travel Market 2023
Scholars, Black History authorities, dignitaries, and influential individuals from the United Kingdom convened at the Ethiopian Embassy in London to mark a momentous occasion – the official registration and recognition of the Global Black History, Heritage, and Education Centre (GBHHEC) in Addis Ababa, Ethiopia. Ambassador Teferi Melesse, addressing the gathering, underscored the profound significance of this historic moment, not only…
28 Oct 2023
GBHHEC official registration celebrated in London
Ethiopians are pleased to host the Great Ethiopian Run on 19 November 2023. International participants from 12+ countries have already registered through our page. Don't miss out – sign up to attend in person here: 2023 Sofi Malt Great Ethiopian Run International 10K | In Person To attend the race here in UK which will being staged in conjunction with…
20 Oct 2023
2023 Sofi Malt Great Ethiopian Run International 10K
Today, at the Ethiopian Embassy in London, we celebrated Ethiopia's 16th National Flag Day with the theme "The Prestige of Our Flag: A Guarantee for Unity and Sovereignty." We paid tribute to the collective sacrifice made "for the love and honor of our flag" to protect our sovereignty. Our flag embodies freedom, unity, and the pride of our people.  
16 Oct 2023
Ethiopian Flag Day.
Press Release on The Tendering of 8 State-owned Sugar Enterprises Notice of Bid Submission on 5th October 2023
13 Oct 2023
Notice of Bid Submission
The 2023 Sofi Malt Great Ethiopian Run International 10km is gearing up to unite runners from around the world. Get ready for a global sporting adventure as athletes from UK, and more converge for an epic race! for further detail: https://bit.ly/3QbDMeN 
11 Oct 2023
Great Ethiopian Run 2023