ኢትዮጵያ ያሏትን የኢንቨስትመንት አማራጮች፣ የካፒታል ገበያንና የሰነደ መዋእለ ነዋይ/ Securities Market/ እድሎችን ለንደን አየተካሄደ ባለው አለም አቀፍ የፋይናንስ ዘርፍ ጉባኤ ላይ አቀረበች፡፡

10 Oct 2023

“ኢንቨስት አፍሪካ 2023” በሚል ለንደን ላይ እየተካሄደ ባለው የአፍሪካ የፋይናንስ ዘርፍ አመታዊ ጉባኤ ላይ ኢትዮጵያ ከኢንቨስትመንት አማራጮች በተጨማሪ ለመጀመሪያ ጊዜ የካፒታል ገበያንና የሰነደ መዋእለ ነዋይ /Securities Market/ እድሎችን ለዩናይትድ ኪንግደም እና ከተለያዩ ሀገሮች ለመጡ በፋይንናስ እና በባንክ ዘርፍ ላይ ለተሰማሩ ባለሃብቶች ሰፊ ማብራሪያ ተሰጥቷል፡፡

10ኛ አመቱን በያዘውና ከመላው አለምና ከአፍሪካ በፋይናንስ ዘርፍ ላይ የተሰማሩ ባለሃብቶችን ያካተተው ኢንቨስት አፍሪካ 2023 ጉባኤ ላይ የገንዘብ ሚኒስቴር ሚንስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሰመሪታ ሰዋሰው የመሩት የልኡክ ቡድን፣ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ወ/ሮ ሌሊሴ ነሜ ፣ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን ፣ የሰነደ መዋእለ ነዋይ እና የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ የስራ ሃላፊዎች እና በዩናይትድ ኪንግደም የኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ተገኝተዋል፡፡

የገንዘብ ሚንሰቴር ሚንስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሰመሪታ ሰዋሰው በጉባኤው ላይ እንደተናገሩት በኮቪድ ፣ በግጭት እና በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት የሚከሰት ድርቅን ተቋቁሞ የኢትየጵያ ኢኮኖሚ ባለፉት ሶስት አመታት ከ 6.1 በመቶ በላይ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን ተናግረዋል፡፡

በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ አጠቃላይ አመታዊ ምርት ከ 126 ቢሊዮን ዶላር በላይ መድረሱን የተናገሩት ሚንስትር ዴኤታዋ የኢኮኖሚ እድገቱ የግሉን ዘርፍ በማካተት ይበልጥ ለማደግ የሚችልበት እድል ተከፍቷል ብለዋል፡፡

በተለይም ሁለተኛው የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም ዋነኛ ትኩረቱ የግሉን ዘርፍ በስፋት በማሳተፍ የተሻለ የኢኮኖሚ እድገትን ለማስዝገብ በቂ ዝግጅት መደረጉን አስረድተዋል፡፡

የፋይናንስ ዘርፉን ለሀገር ውስጥና ለውጪ ባለሃብቶች ክፍት ማድረግ ፣ የንግድና ኢንቨስትመንት ማነቆዎችን በመፍታት የተሳለጠ ምቹ ሁኔታን መፍጠር ፣ በግብርና ፣ በማንፋክቸሪነግ፣ በቱሪዝም ፣ በማእድን እና በአይሲቲ ዘርፍ ሰፊ እድሎች መመቻቸታቸውን ተናግረዋል፡፡

ከዚህ ቀደም ያልነበሩ በአሁኑ ወቅት ግን የመንግስት የልማት ድርጅቶች ድርሻ 25 በመቶ ቀሪው ድርሻ ደግሞ በሀገር ውስጥና በውጪ ባለሃብቶች የሚሸፈንበት የፋይናንስ ኢንቨስትመንት ዘርፍ፣ የሰነደ መዋእለ ነዋይ /Securities Market/ በቅርቡ ይፋ መደረጉን አስታውሰው እነዚህ እድሎች ከፍተኛ የፋይናንስ ባለሃብቶችን በመሳብ ረገድ ሰፊ ሚና እንዳላቸው በመግለጽ ባለሃብቱ በዚህ ዘርፍ እንዲሰማራም ጥሪ አቅርበዋል፡፡

አያይዘውም የባንክ የህግና የቁጥጥር ስርአት ዝግጅቱ በመከናወኑ የባንክ ዘርፉን ለውጪ ባለሃብቶች ክፍት ለማድረግ ዝግጅት መጠናቀቁን ተናግረዋል፡፡

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽነር ወ/ሮ ሊሊሴ ነሜ በበኩላቸው በአሁኑ ወቅት የኢንዱስትሪ ፓርኮች የአንድ መስኮት አገልግሎት እየሰጡ መሆናቸውን፣ ባለሃብቱ በማንፋክቸሪንግ ፣ በግብርና ፣ በፋርማሲዩቲካል ፣ በቱሪዝም ፣ በአይሲቲ ፣ በማእድን ዘርፎቸ ላይ ቢሰማራ ትርፋማ ሊሆን እንደሚችል ገልጸዋል፡፡

የኢንቨስትመንት ህጎችና መመሪያዎች አለም አቀፍ ደረጃቸውን ጠብቀው እንዲሰሩ ለማድረግ በየወቅቱ ማሻሻያ እየተደረገባቸው መሆኑን አስረድተው ኢትዮጵያ ካላት ምቹ የገበያ ፣ የጉልበት እና የጥሬ እቃ አቅርቦት አንጻር ተመራጭ እንደሆነች አስገንዝበዋል፡፡

በዩናይትድ ኪንግደም የኢትዮጵያ መንግስት ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ተፈሪ መለሰ በሌላ በኩል እንደተናገሩት ኢትዮጵያ ለአለም አቀፍ ገበያ ስትራቴጂካዊ ቦታ ላይ እንደምትገኝ ገልጸው ፣ መላው አለምን ሊያገናኝ የሚችል የአየር መንገድ እና የካርጎ አገልግሎት ያላት ፣ በቂና የሰለጠነ ወጣት የሰው ሃይል የታደለች ፣ሸማች የሆነ ማህበረሰብ ያላት መሆኗ ተመራጭነቷን ያጎላዋል ብለዋል፡፡

ኢትዮጵያ በርካታ የኢኮኖሚ ፣ የፋይናንስ፣ የቴሌኮም፣ የህግና የተቋማት ሪፎርሞችን በማካሄዷ የዩናይትድ ኪንግደም ታላላቅ ኩባኒያዎች በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ላይ መሰማራት መቀጠላቸውን አስታውሰው ኤምባሲው ለባለሃብቶች የሚሰጠውን አገልግሎት ከምንጊዜውም በላይ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አሰረድተዋል፡፡

የዩናይትድ ኪንግደም ኢንተርናሽናል ኢንቨስትመንት መስሪያ ቤት የስራ ሃላፊዎችም በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ላይ ለሚሰማሩ ባለሃብቶች አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን በጉባኤው ላይ ተናግረዋል፡፡

“ኢንቨስት አፍሪካ 2023” አለም አቀፍ ጉባኤ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ የገንዘብ ሚኒሰቴር ሚንስትር ዴኤታ የመሩት ልኡክ ዛሬን ጨምሮ ለሚቀጥሉት ሁለት ቀናት በአማራጮች ላይ ከባለሃብቶች ጋር የቡድንና የግል ውይይታቸውን ማድረጋቸውን ይቀጥላሉ፡፡

 

Latest News

Browse all
በኤፕሪል 1973 ወደ ዩናይትድ ኪንግደም በረራውን ቦይንግ 720-ቢ አውሮፕላን በመጠቀም በሳምንት ለሁለት ቀናት የጀመረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአሁኑ ወቅት አጅግ ዘመናዊ የሆኑ ኤርባስ 350 እና ቢ787 ድሪምላይነር አውሮፕላኖችን በመጠቀም በሳምንት ለአስር ጊዜያት በቀጥታ በረራ እያካሄደ መሆኑ ተመልክቷል፡፡ በዚህም ከአስር ሺህ በላይ መንገደኞችን ወደ 60 አለም አቀፍ መዳረሻዎች እያጓጓዘ መሆኑን በዩናይትድ ኪንግደም እና አየርላንድ የአየር መንገዱ ጽ/ቤት አስታውቋል፡፡ በለንደን ሂትሮ እና…
23 Nov 2023
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ዩናይትድ ኪንግደም የሚያደርገውን በረራ በሳምንት ወደ አስር ጊዜያት ማሳደጉን አስታወቀ፡፡
On the sidelines of the Global Food Security Summit the Ethiopian Ambassador to UK H.E. Ambassador Teferi Melesse Desta met with British International Investment and AgDevCo to discuss potential investment and collaboration in Ethiopia. The Ambassador commended the work done with EthioChicken and explained the robust potential Ethiopia has attract even more investment.
21 Nov 2023
Ambassador Teferi met with BII and AgDevCo
We are excited to announce the inaugural flight of Ethiopian Airlines from Addis Ababa to Gatwick Airport landed earlier today! This new route marks an important milestone in Ethiopian Airlines commitment to providing convenient and seamless travel options for passengers between the UK and Ethiopia. We look forward to welcoming you on board as we connect the vibrant city of…
21 Nov 2023
Ethiopian Airlines Started new route to London Gatwick Airport.
“We have no intention of threatening the sovereignty of any nation but we would like a rules based access to the Red Sea. Our request is to initiate discussions towards sustainable solutions.” “What we seek to accomplish as a nation requires clarity of thought. It also requires hard work on a daily basis. Although there are many issues contributing to…
14 Nov 2023
PM Abiy Ahmed Responds to MP’s
For all diaspora scholars interested in participating in technical and vocational colleges' short-term knowledge and skill transfer programs. Click the link for further detail: https://t.co/p5ExO5oiLn  or Download the PDF format: Document.
8 Nov 2023
Notice for Diaspora Scholars
ከ 184 በላይ የአለም ሀገራት በተሳተፉበትና በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ጎብኚዎች ፣ አለም አቀፍ እውቅና ያላቸው የተለያዩ ሀገራት አሰጎብኚዎች እና የጉዞ ጸሀፍት በተገኙበት በዚሁ አለም አቀፍ የጉዞ የገበያ ማእከል ኢትዮጵያ አለም አቀፍ እውቅና ካገኙ የቱሪስት ሀብቶቿ ጀምሮ አዳዲስ የቱሪስት መዳረሻዎቿን አስተዋውቃለች፡፡ የቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር አምባሳደር ናሲሴ ጫሊ ፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ፣የክልል ቱሪዝም ቢሮዎች ፣ ከ 16 በላይ የኢትዮጵያዊያን አስጎብኚ ድርጅቶች፣ ዳያስፖራውና…
7 Nov 2023
ኢትዮጵያ አዳዲስና ጥንታዊ የቱሪስት ሀብቷን ለንደን ኤክሴል በሚገኘው አለም አቀፍ የጉዞ ገበያ ማእከል ላይ አስተዋወቀች፡፡
The 42nd World Travel Market London 2023 Officially kicked off today at ExCeL London with the presence of H.E. Nasise Challi Jira of Ministry of Tourism-Ethiopia, H.E. Ambassador Teferi Melesse Desta of Embassy of Ethiopia, London, Mr. Henok from Ethiopian Airlines, Hailemelekot Mamo, v/p ET Holidays and Digital services and different tour operators from Ethiopia. It's being visited by multitude…
6 Nov 2023
World Travel Market 2023
Scholars, Black History authorities, dignitaries, and influential individuals from the United Kingdom convened at the Ethiopian Embassy in London to mark a momentous occasion – the official registration and recognition of the Global Black History, Heritage, and Education Centre (GBHHEC) in Addis Ababa, Ethiopia. Ambassador Teferi Melesse, addressing the gathering, underscored the profound significance of this historic moment, not only…
28 Oct 2023
GBHHEC official registration celebrated in London
Ethiopians are pleased to host the Great Ethiopian Run on 19 November 2023. International participants from 12+ countries have already registered through our page. Don't miss out – sign up to attend in person here: 2023 Sofi Malt Great Ethiopian Run International 10K | In Person To attend the race here in UK which will being staged in conjunction with…
20 Oct 2023
2023 Sofi Malt Great Ethiopian Run International 10K
Today, at the Ethiopian Embassy in London, we celebrated Ethiopia's 16th National Flag Day with the theme "The Prestige of Our Flag: A Guarantee for Unity and Sovereignty." We paid tribute to the collective sacrifice made "for the love and honor of our flag" to protect our sovereignty. Our flag embodies freedom, unity, and the pride of our people.  
16 Oct 2023
Ethiopian Flag Day.
Press Release on The Tendering of 8 State-owned Sugar Enterprises Notice of Bid Submission on 5th October 2023
13 Oct 2023
Notice of Bid Submission
The 2023 Sofi Malt Great Ethiopian Run International 10km is gearing up to unite runners from around the world. Get ready for a global sporting adventure as athletes from UK, and more converge for an epic race! for further detail: https://bit.ly/3QbDMeN 
11 Oct 2023
Great Ethiopian Run 2023